የሀገር ውስጥ ዜና

ዩኒቨርሲቲው በጦርነቱ ምክንያት የተፈጠረውን የስነ ልቦና ችግር ለመፍታት ለማህበረሰቡ ስልጠና ሊሰጥ ነው

By Feven Bishaw

January 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወሎ ዩኒቨርሲቲ በጦርነቱ ምክንያት የተፈጠረውን የስነ ልቦና ችግር ለመፍታት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለአካባቢው ነዋሪዎች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ገለፀ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ÷ በአሁኑ ወቅት የማህበረሰብ ስነ ልቦና ግንባታ ስልጠና አስፈላጊ ነው ያሉ ሲሆን÷ በጦርነቱ ምክንያት ከወደመው ቁሣቁስ በላይ የተፈጠሩ የስነ ልቦና ጉዳቶች ለመጭው የልማት እንቅስቃሴ እንቅፋቶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡