የሀገር ውስጥ ዜና

100 በጎ ፈቃደኛ የጤና ባለሙያዎች ለሕክምና ድጋፍ ወደ አማራ ክልል ተሰማሩ

By Feven Bishaw

January 30, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)በጦርነቱ ጉዳት ለደረሰባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ የሕክምና ድጋፎች ለመስጠት አንድ መቶ በጎ ፍቃደኛ የጤና ባለሙያዎች ወደ አማራ ክልል ተሰማሩ።

የሕክምና ባለሙያዎቹ ከጥር 22 እስከ 29 ቀን 2014 በአማራ ክልል የሕክምና ምርመራ፣ ሕክምናና የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ፤ መድኃኒትም ያቀርባሉ ተብሏል።