የሀገር ውስጥ ዜና

የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ለኢትዮጵያ 13 ሚሊየን ዶዝ የኮቪድ-19 ክትባት ለገሱ

By Meseret Awoke

January 31, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ለኢትዮጵያ 13 ሚሊየን ዶዝ የኮቪድ-19 ክትባት ለገሱ።

ድጋፍ ካደረጉ የአባል አገራቱ መካከልም ፈረንሳይ፣ ፊንላንድ፣ ዴንማርክ፣ ግሪክ፣ ጣልያን እና ስዊድን ይገኙበታል፡፡

ድጋፉም የጤና ሚኒስቴር በመላው ኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ስርጭት ለማዳረስ የሚያደርገውን ጥረት እንደሚያግዝ ተገልጿል፡፡

ከዚህ ቀደም የተለያዩ የአውሮፓ አባል አገራት ከ24 ሚሊየን ዶዝ በላይ የኮቪድ-19 ክትባት ለኢትዮጵያ መለገሳቸውን በኢትዮጵያ ከሚገኘው የፈረንሳይ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!