የሀገር ውስጥ ዜና

የሶማሌ ክልል “መመረጥ ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ ጀመረ

By Feven Bishaw

January 31, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ብልፅግና ፓርቲ “መመረጥ ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ” በሚል መሪ ሀሳብ የአመራር ግንባታ የውይይት መድረክ በጅግጅጋ ከተማ ማካሄድ ጀመረ፡፡

በመድረኩ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድን ጨምሮ የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ኡስማን እና የሶማሌ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ ኢንጅነር መሀመድ ሻሌ ተገኝተዋል።