አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ በክልል ከፍተኛ አመራር ደረጃ የአመራር ግንባታ መድረክ ሀዋሳ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
የመድረኩን ዋና ዓላማና ትኩረትን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ጽኅፈት ቤት ኃላፊ አብርሃም ማርሻሎ፥ የምክክር መድረኩ መሪ ቃልና ዋና የሃሳቡ ማጠንጠኛ የሚሆነው “መመረጥ – ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ ” ነው በሚል በተዘጋጀ ሰነድ ላይ እንደሆነ አንስተዋል።