አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል “መመረጥ ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጸጋዬ ማሞ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን፥ ለመድረኩ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡