የሀገር ውስጥ ዜና

የደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል “መመረጥ ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ እያካሄደ ነው

By Feven Bishaw

February 01, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ምዕራብ የኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል “መመረጥ ተለውጦ ሀገርን ለመለወጥ” በሚል መሪ ቃል የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እያካሄደ ነው፡፡

በመድረኩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾን ጨምሮ የክልሉ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ጸጋዬ ማሞ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን፥ ለመድረኩ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡