አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዲሱን ትውልድ በንባብ የዳበረ ዕውቀት እንዲኖረው ደረጃቸውን የጠበቁ ቤተ መጻህፍት ማስፋፋት እንደሚገባ አምባሳደር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ አመለከቱ።
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከ106 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያስገነባው ዘመናዊ ሁለገብ ቤተ መጻህፍት ዛሬ የተመረቀ ሲሆን÷ በየኒቨርሲቲው ሥር ለተቋቋመው ለኢትዮጵያ ቴክስታይል፣ ፋሽንና ቴክኖሎጂ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።