አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች በ2011 ዓ.ም አፅድቀውት የነበረውን የመወያያ መመሪያ ሰነድ ማሻሻያ በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረጉበት በኋላ በድጋሚ እንዲፀድቅ አድርገዋል፡፡
መመሪያ ሰነዱ፥ በፓርቲዎች መካከል የሚደረግን ውይይት በስነ ምግባር የታገዘ እንዲሆን እና አስፈላጊ ከሆነው ፉክክር ውጪ የሚታየውን ያለመተማመን ለማስወገድ እንደሚረዳም ተገልጿል፡፡