የሀገር ውስጥ ዜና

ቦርዱ በፓርቲዎች መካከል የሚደረጉ ውይይቶች የሚመሩበት መመሪያ ሰነድን አፀደቀ

By Feven Bishaw

February 02, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፖለቲካ ፓርቲዎች በ2011 ዓ.ም አፅድቀውት የነበረውን የመወያያ መመሪያ ሰነድ ማሻሻያ በማድረግ ሰፊ ውይይት ካደረጉበት በኋላ በድጋሚ እንዲፀድቅ አድርገዋል፡፡

መመሪያ ሰነዱ፥ በፓርቲዎች መካከል የሚደረግን ውይይት በስነ ምግባር የታገዘ እንዲሆን እና አስፈላጊ ከሆነው ፉክክር ውጪ የሚታየውን ያለመተማመን ለማስወገድ እንደሚረዳም ተገልጿል፡፡