አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተፈጥሮና በሰብዓዊ ሀብት የታደለችው አፍሪካ ለዜጓቿ ምቹ እንድትሆን የአባል ሀገራቱን የእኮኖሚ ነጻነት ማረጋገጥ ይገባል ሲሉ ምሁራን ተናገሩ፡፡
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ዶክተር መሳይ ሙሉጌታ እና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ዶክተር መላኩ ተገኝ÷ አህጉሪቱ ለሌሎች አህጉራት የሚተርፍ ሀብት ይዛ ዜጓቿ ግን አሁንም በድርቅእና በረሃብ ይሰቃያሉ ብለዋል፡፡