የሀገር ውስጥ ዜና

ሥራ ፈጣሪና ሀብት አመንጭ ለሆኑ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል- ዶክተር በለጠ ሞላ

By Feven Bishaw

February 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ጥር 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቴክኖሎጂ ዘርፍ ሥራ ፈጣሪና ሀብት አመንጭ ለሆኑ ጀማሪ የቴክኖሎጂ ፈጣራዎች እና እምቅ አቅምና ክህሎት ላላችው ድጋፍና ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል ሲሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ ገለጸ፡፡

የአገር አቀፍ የፈጠራ ባለሙያዎችና የስታርታፖች መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷የኢኖቬሽን ምርምር ድጋፍ ማመልከቻና ማሳወቂያ ፓርታል ተመርቋል፡፡