የሀገር ውስጥ ዜና

በ4 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የአራት የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ውል ተፈረመ

By Tibebu Kebede

February 20, 2020

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 12 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ለ4 የመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ የ4 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር በላይ ውል ስምምነት ከተለያዩ ተቋራጮች ጋር ተፈራረመ።

በውል ስምምነቱ ላይ የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንዲሁም መንገድ ከሚገነባባቸው አካባቢዎች የተወከሉ የሃገር የሽማግሌዎች ተገኝተዋል።