አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ35ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ጋር ቆይታ ማድረጋቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ እንደተናገሩት÷ ከጉባኤው ጎን ለጎን በተካሄደው የመሪዎቹ የሁለትዮሽ ምክክር ላይ የሀገራቱን ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ መክረዋል።