አዲስ አበባ፣ የካቲት1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የሚጀምር መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር አበበ ግርማ ገለጹ።
በአሸባሪው ህወሃት ውድመትና ዘረፋ የተፈፀመበት የወልድያ ዩኒቨርሲቲ የመልሶ ጥገና ስራ በማከናወን ከየካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የማታ ተማሪዎችን በመቀበል ስራውን የሚጀምር ሲሆን÷ በተከታይም የመጀመሪያ አመትና ተመራቂ ተማሪዎችን ይቀበላል ተብሏል።