የሀገር ውስጥ ዜና

በብዙዎች ዘንድ ‘ግራንድ ፒ’ በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ሙሳ ሳንዲያና ካባ አንድነት ፓርክን ጎበኘ

By Melaku Gedif

February 09, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት ኢትዮጵያን ለመጎብኘት የመጣውና በብዙዎች ዘንድ ‘ግራንድ ፒ’ ተብሎ የሚታወቀው ጊኒያዊው አርቲስት ሙሳ ሳንዲያና ካባ አንድነት ፓርክን ጎበኘ፡፡

“ግራንድ ፒ” ትናንት አዲስ አበባ ሲገባ አትዮጵያውያን አድናቂዎቹ ደስታቸውን የገለጹለት ሲሆን÷ በዛሬው ዕለትም አንድነት ፓርክን ጎብኝቷል፡፡

አርቲስቱ በሙዚቃ፣ ፖለቲካ እና በትወና ዘርፎች ባለው ችሎታ ከአገሩ ከጊኒ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂነትን አትርፏል፡፡

“ኢንዲፐንደንስ” በሚል ሙዚቃውም ይታወቃል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!