የሀገር ውስጥ ዜና

ከ106 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

By Feven Bishaw

February 12, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባሳለፍነው ሳምንት ከ106 ሚሊየን 170 ሺህ ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የገቢና የወጪ የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ኮሚሽኑ ባሳለፍነው ሳምንት ባደረገው ክትትል ነው 92 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች እና 13 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባንድ እቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የተያዙት፡፡