አዲስ አበባ፣ የካቲት 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ባለፉት ሁለት ሳምንታት 86 በረራዎችን በማድረግ ከ110 ሚሊየን በላይ የአበባ ዘንግ ወደተለያዩ ሀገራት ማጓጓዙን አስታወቀ።
እንደ ዓየር መንገዱ ገለፃ የአበባ ዘንጎቹን በዋናነት ከኢትዮጵያ ወደ ተለያዩ ሀገራት ቢያጓጉዝም፥ በተጨማሪም ምርቱን ከኬንያ፣ ኢኳዶር፣ ኮሎምቢያና ሚያሚ (ዩናይትድ ስቴትስ) ወደ ተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት አጓጉዟል።