የሀገር ውስጥ ዜና

በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ18 ሺህ በላይ ጥይትና ሽጉጥ ተያዘ

By Feven Bishaw

February 15, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ እና ከሳንጃ ወደ ጎንደር ሊገባ የነበረ ከ18 ሺህ በላይ ጥይትና ሽጉጦች መያዙን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ፡፡

የመምሪያው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኮማንደር ውብነህ አስናቀ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በሁለት ባለሾስት እግር ተሸከርካሪዎች ውስጥ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጦች፣ 18 ሺህ 200 የሽጉጥ ጥይቶች ተይዘዋል፡፡