አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኑሮ ውድነቱን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በዚህም በየሳምንቱ መጨረሻ በአዲስ አበባና ድሬዳዋ የተጀመሩትን አምራች እና ሸማችን በቀጥታ የማገናኘት ተግባር በሁሉም ክልሎች እንዲቀጥል እየተሰራ መሆኑን ነው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሃመድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለፁት፡፡