አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል ርዕሰ መሰተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ የሚመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራር ቡድን ደረጃውን በጠበቀ መልኩ በ155 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባውን የሀርተሼክ-ሀርሺን የጠጠር መንገድ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን አስደረገ።
በሶማሌ ክልል መስኖና ተፋሰስ ልማት ቢሮ የተገነባው የሀርተሼክ-ሀርሽን ጠጠር መንገድ ፕሮጀክት በተያዘለት በጀትና የጊዜ ገደብ የተጠናቀቀ ሲሆን፥ በክልሉን ሦስት ዞኖች የሚገኘውን ህዝብ የሚያስተሳስር መሆኑ ተገልጿል።