አዲስ አበባ፣ የካቲት 10 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በክልሉ ድህነትን ለመቀነስና እና የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
በክልሉ ሁለተኛው ዙር የከተማ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በይፋ የተጀመረ ሲሆን÷ በመድረኩ ላይ ተገኙት የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ፥ ስር የሰደደ ድህነትን ለመቀነስ እና የስራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡