አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ኢትዮጵያን በተመለከተ የተዘጋጀው ኤች አር 6600 የውሳኔ ሀሳብ እንዳይጸድቅ በኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተጀመረው ጥረት መቀጠሉ ተገለፀ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ አሜሪካ የዜጎች ምክር ቤት የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አምሳሉ ካሳው እንደተናገሩት ፥ ሂደቱን ለመቃወም እስካሁን ለ790 የአሜሪካ የምክር ቤት አባላት እና ባልደረቦቻቸው ባለ አስር ነጥብ የተቃውሞ ደብዳቤ በእጃቸው እንዲደርሳቸው ተደርጓል።