አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል በታታ ሀይቅ ላይ የተከሰተውን እንቦጭ አረም የማስወገድ መርሃ ግብር የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተጀምሯል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይ አቶ ጁል ናንጋል፥ አረሙ በዓሳ ሀብት ላይ ከፍተኛ ችግር የሚፈጥር መሆኑን አመልክተው አረሙ በበለጠ ከመስፋፋቱ በፊት መላው የክልሉ ህዝብና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለመከላከል ጥረት እንዲያደረጉ አሳስበዋል።