አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በድርቅ ለተጎዱ ሁለት ወረዳዎች ከ2 ሺህ 200 ኩንታል በላይ የምግብ እህል ድጋፍ ማድረጉን የዞኑ አደጋ ስጋት አመራርና ልማት ተነሺዎች ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡
የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ አልፊያ አልዪ እንዳሉት ÷ በዞኑ ሀዊ ጉዲና እና ቡርቃ ዲምቱ ወረዳዎች በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች የተደረገው ድጋፍ ከዞኑና ከሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ነዋሪዎች የተሰበሰበ ነው።