የሀገር ውስጥ ዜና

በወላይታ ሶዶ ከተማ ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ ሆስፒታል ተመረቀ

By Feven Bishaw

February 19, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የእንያት ሆስፒታል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ፡፡

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትሯ ተወካይ ዶክተር አባስ ሁሴን፥ በኢትዮጵያ ላለፉት አመታት መከላከልን ማዕከል ባደረገ፣ ሕክምናን ለማሻሻልና ለማስፋፋት ከፍተኛ ጥረት መደረጉንና በዚህም አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለፁት።