አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የእንያት ሆስፒታል ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ፡፡
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትሯ ተወካይ ዶክተር አባስ ሁሴን፥ በኢትዮጵያ ላለፉት አመታት መከላከልን ማዕከል ባደረገ፣ ሕክምናን ለማሻሻልና ለማስፋፋት ከፍተኛ ጥረት መደረጉንና በዚህም አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ነው የገለፁት።