አዲስ አበባ፣ የካቲት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ገምግሞ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ለስድስት አንጋፋና ወጣት ተመራማሪዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አለምእሸት ተሾመ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት÷ የዩኒቨርሲቲ ው አስተዳደር ቦርድ ዛሬ የካቲት 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ገምግሞ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ለስድስት አንጋፋና ወጣት ተመራማሪዎቹ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡