የሀገር ውስጥ ዜና

በጦርነት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ ለማቋቋም 58 ከተሞች የጥምረት ስምምነት ተፈራረሙ

By Feven Bishaw

February 21, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦርነት የወደሙና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ ለማቋቋም 58 ከተሞች የጥምረት ስምምነት መፈራረማቸውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ የመገባንት ሂደት በተፋጠነ መልኩ ለማስኬድ የሚያግዝ አሰራር መዘርጋቱንም አስታውቋል።