የሀገር ውስጥ ዜና

የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ምክር ቤት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆች ላይ ውይይት አደረገ

By Feven Bishaw

February 22, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ምክር ቤት የተለያዩ ረቂቅ አዋጆች ላይ ውይይት በማድረግ ለጨፌ ኦሮሚያ መምራቱን የክልሉ የመንግስት ኮምንኬሽን ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮ ሀላፊው አቶ ሀይሉ አዱኛ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የክልሉ አስተዳደር ምክር ቤት አራት ረቂቅ አዋጆች ላይ ውይይት በማድረግ ወደ ጨፌ ኦሮሚያ መርቷል ብለዋል።