አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ድህረ ታላቁ ጉዞ ወደ ሀገር ቤት የዳያስፖራ ተሳትፎን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኮረና የፌዴራል ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የኢፌዴሪ ሚሲዮኖች የተሳተፉበት የበይነ መረብ ውይይት ተካሄደ።
በውይይቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፥ ዳያስፖራው ኢትዮጵያ በችግር ውስጥ በነበረችባቸው አስጨናቂ ጊዜዎች ላደረገው ድጋፍና ላስገኛቸው ውጤቶች ምስጋና አቅርበው አሁንም ሀገራዊ ፈተናዎቹ እስኪወገዱ ድረስ ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሚሲዮኖችና ባለድርሻ አካላት በጋራ መስራታቸውን እንዲያጎለብቱ አሳስበዋል፡፡