አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ እና የሩስያ የኢኮኖሚ ትብብር ማስተባበሪያ ኮሚቴ ጽህፈት ቤት (አፍሮኮም) ጽህፈት ቤቱን በአዲስ አበባ ከፈተ፡፡
በመክፈቻ ስነ ስርአቱ ላይ የሩሲያ የፌደሬሽን ምክር ቤት አባል ሴናተር ኢጎር ሞሮዞቭ፣ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጀኒ ተረሂን እና የሃይማኖት አባቶችን የወከሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የውጭ ግንኙነት የበላይ ሃላፊ ብጹዕ አቡነ አረጋዊ እና የመንግስት ሃላፊዎች ተገኝተዋል።