አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሶስትዮሽ ውይይት ውጪ ሌሎች ምክረ ሀሳቦችን እንደማትቀበል የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ገለፁ።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው ዕለት ለካቢኔ አባላት እና ለባለድርሻ አካላት የግድቡን አሁናዊ ገፅታ እና በግብፅ ወቅታዊ አቋም ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል።