አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በየም ልዩ ወረዳው ሳጃ ከተማ አስተዳደር በ54 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ከሳጃ ላፍቴን ኮሾ ድረስ የሚገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ሳይት ከተቋራጮች ጋር ርክክብ ተካሂዷል፡፡
በሳይት ርክክቡ የተገኙት የልዩ ወረዳው ውሃና ማዕድን ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጂሀድ ሳንቢ ፥ የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ ግብርናውን ማዘመን እንደሚገባ ገልጸው ፥ ለዚህም የመስኖ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡