የሀገር ውስጥ ዜና

በ54 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ለሚገነባው የኮሾ መስኖ ፕሮጀክት ሳይት ከተቋራጮች ጋር ርክክብ ተደረገ

By Feven Bishaw

February 25, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በየም ልዩ ወረዳው ሳጃ ከተማ አስተዳደር በ54 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ከሳጃ ላፍቴን ኮሾ ድረስ የሚገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ሳይት ከተቋራጮች ጋር ርክክብ ተካሂዷል፡፡

በሳይት ርክክቡ የተገኙት የልዩ ወረዳው ውሃና ማዕድን ኢነርጂ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጂሀድ ሳንቢ ፥ የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ ግብርናውን ማዘመን እንደሚገባ ገልጸው ፥ ለዚህም የመስኖ ልማት ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡