አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀረር ከተማ በሚገኘው ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ህይወት ፋና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የተገነባው የካንሠር ህክምና መስጫ ማዕከል ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ።
የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ለህንፃ ግንባታው ከ65 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ያደረገበት ሲሆን፥ ለማዕከሉ የሚያስፈልጉ የጨረር ህክምና መስጫ መሳሪያዎችን ደግሞ የጤና ሚኒስቴር ከአጋሮቹ ጋር በመተባበር ከ4 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ አሟልቷል።