አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በእነ ጌታቸው አሰፋ መዝገብ የተከሰሱት የቀድሞ የብሔራዊ መረጃ ደህንነት ሰራተኞችን የመከላከያ ማስረጃ ለመጠባበቅ ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ተገልጿል፡፡
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ለከሳሾቹ ከዚህ በፊት ፈቅዶላቸው የነበረው የ30 ሺህ ብር ዋስትና መብት ባሳለፍነው ሳምንት የካቲት 16 /2014 ዓ/ም በጠቅላይ ፍርድ ቤት 1ኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት ተሽሮ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ መወሰኑ ይታወሳል።