ዓለምአቀፋዊ ዜና

ቻይና በድርቅ ለተጎዱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደምታደርግ አስታወቀች

By Feven Bishaw

March 01, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በድርቅ ለተጎዱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደምታደርግ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ገለጹ።

ሃገሪቱ በድርቅ ጉዳት ለደረሰባቸው የአካባቢው ሀገራት አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደምታደርግ ከሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዲሳኢድ ሙሳ አሊ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት ገልጸዋል፡፡