የሀገር ውስጥ ዜና

ሚሲዮኑ 139 ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ድጋፍ አደረገ

By Feven Bishaw

March 01, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታለው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ የኬንያን ድንበር በህገወጥ አቋርጠው የገቡ 139 ኢትዮጵያውያንን ሚሲዮኑ በምህረት ክሳቸው ተቋርጦና ከእስር ቤት ተፈተው ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ ድጋፍ አድርጓል።

ኢትዮጵያውያኑ በኪያምቡ፣ ጊጊሪ፣ ፓንጋኒ፣ ጆጎ፣ ቡሩቡሩ እና ዳንዶራ እስር ቤቶች በእስር ከአንድ እስከ ዘጠኝ ወር ድረስ የቆዩ ናቸው።