የሀገር ውስጥ ዜና

ዐድዋ የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ፋና እና የሰዎች እኩልነት ምልክትና ምሳሌ ነው – አቶ ዣንጥራር አባይ

By Feven Bishaw

March 02, 2022

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዐድዋ የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ፋና፣ የነጮችን የዘመናት የበላይነት የገታ፣ የሰዎች እኩልነት ምልክትና ምሳሌ የኢትዮጵያውያን አኩሪ ገድል ውጤት መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ዣንጥራር አባይ ተናገሩ።

ምክትል ከንቲባው በ126ኛው የዐድዋ ድል በአል ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።