የሀገር ውስጥ ዜና

የክተት አዋጅ በታወጀባት ወረኢሉ ከተማ 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል ተከበረ

By Feven Bishaw

March 02, 2022

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዳግማዊ አፄ ሚኒልክ የክተት አዋጅ ባወጁባት ወረኢሉ ከተማ 126ኛው የዓድዋ ድል በዓል በድምቀት ተከብሯል።

በድል በዓሉ ላይ የተገኙት በመከላከያ ኢንጅነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ሀላፊ ሜጀር ጀኔራል አህመድ ሀምዛ፥ የኢትዮጵያውያን ጠንካራ የአንድነት መንፈስ ማሳያ፣ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ውል የሆነው ዓድዋ የአንድነታችን እንጅ የልዩነታችን ምክንያት ሊሆን አይገባም ብለዋል።