አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) መደበኛ አገልግሎት መስጠት የጀመረውን የኮምቦልቻ ወደብና ተርሚናል ቀድሞ ወደ ነበረበት አቋም ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሮባ መገርሳ እንደገለጹት÷ ወደቡ በነበረው ጦርነት ውድመት ከደረሰበት በኋላ እንደገና ስራ ለማስጀመር ድርጅቱ በወሰደው አፋጣኝ እርምጃ ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡