የሀገር ውስጥ ዜና

በኦሮሚያ ክልል ከ13 ቢሊየን ብር በላይ በጀት የመስኖ ግድቦች ግንባታ እየተካሄደ ነው

By Feven Bishaw

March 05, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ግብርናውን ከዝናብ ጠባቂነት ለማላቀቅ ከ13 ቢሊየን ብር በላይ በጀት መካከለኛና አነስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እየተካሄደ መሆኑ ተገለጸ።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊስ አማካሪ አምባሳደር ግርማ ብሩ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍፁም አሰፋና የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ዛሬ በምስራቅ ሸዋ ዞን ሊበን ጭቋላና ወንጂ ኩሩፍቱ በበጋ መስኖ የለማውን የስንዴ ማሳ ጎብኝተዋል።