አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ከተማ ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን ሲያባዙ ነበር የተባሉ 2 የውጭ አገር ዜጎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ፡፡
የክልሉ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ እንዳሉት ÷ግለሰቦቹ የናይጀሪያ እና የኮንጎ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ÷ኅብረተሰቡ ባደረሰው ጥቆማ መሰረት የፌደራልና የክልሉ ፖሊስ በግለሰቦቹ ላይ ክትትል በማድረግ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል።