የሀገር ውስጥ ዜና

በጋምቤላ ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን በማባዛት የተጠረጠሩ 2 የውጭ አገር ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

By Feven Bishaw

March 05, 2022

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ከተማ ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን ሲያባዙ ነበር የተባሉ 2 የውጭ አገር ዜጎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ፡፡

የክልሉ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡገቱ አዲንግ እንዳሉት ÷ግለሰቦቹ የናይጀሪያ እና የኮንጎ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ÷ኅብረተሰቡ ባደረሰው ጥቆማ መሰረት የፌደራልና የክልሉ ፖሊስ በግለሰቦቹ ላይ ክትትል በማድረግ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ውለዋል።