የሀገር ውስጥ ዜና

124ኛውን የአድዋ ድል በዓል ለመዘከር የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት የአድዋ ጉዞ ተጀመረ

By Tibebu Kebede

February 25, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር 124 ኛውን የአድዋ ድል በዓል ለመዘከር ያዘጋጀው የአድዋ ጉዞ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።

በመነሻ ዝግጅቱ ላይ የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳውን ጨምሮ የተለያዩ የመንግሰት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።