የሀገር ውስጥ ዜና

በሩሲያ-ዩክሬን ቀውስ በመከረው የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ወንበሯን ባዶ በማድረግ ስብሰባውን ማለፏ በበሳል የዲፕሎማሲ ውሳኔ የተደረገ ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

By ዮሐንስ ደርበው

March 10, 2022

የአሜሪካ አምባሳደር ትሬሲ ዴቪድሰንም አገራቸው ኢትዮጵያ ሰላምን ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት ማድነቃቸውንና አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ግንኘነቷን ማጠናከር እንደምትፈልግ መግለጻቸውን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

ለሊባኖስ መንግስት የህዳሴ ግድቡን በተመለከተ በአረብ አገራት ዙሪያ የሚስተዋለውን የተሳሳተ ግንዛቤ ማስተካከል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ገለጻ መደረጉን ጠቅሰዋል።

ከሁለትዮሽ እና የንግድ ግንኙነት ጋር በተያያዘም የጂቡቲን የካርጎ አገልግሎት ማፋጠን የሚያስችል ስምምነት መፈጸሙን ጠቁመዋል።

ከዚህ ባለፈም ከቱርክ ጋር በንግድ እና በኢንቨስትመንት ግንኙነትን ማጠናከር የሚያስችል ምክክር ተካሂዷልም ብለዋል።

ከዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ጋር በተያያዘም ዜጎችን ከሳዑዲ ለመመለስ ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን አስረድተዋል።

በመግለጫው ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በጋራ ጉዳዮች ላይ በመደጋገፍ ግንኙነታቸውን እያሳደጉ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን፥ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ አጋርነታቸውን እያሳዩም  ነው ተብሏል።

የሁለቱ አገራት ግንኙነት ለአካባቢው ሰላም እና ትብብር ወሳኝ መሆኑን ያነሱት አምባሳደር ዲና፥ በሰሜኑ የአገሪቱ ክፍል የተፈጠረው ሁኔታ በሁለቱ አገራት ግንኙነት ላይ የተወሰነ እንቅፋት መፍጠሩንም አመላክተዋል።

የሩሲያ እና ዩክሬን ጉዳይን በተመለከተ ኢትዮጵያ የያዘችው አቋም ጥቅሟን የሚያስጠብቅ ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፥ የአምባሳደሮችን አመዳደብ በተመለከተ ኢትዮጵያ ከየአገራቱ ጋር ያላትን የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተቀማጭ በሆኑ፣ ተቀማጭ ባልሆኑ እና በአነስተኛ የሰው ሃይል በሚደገፉ አምባሳደሮች ለማከናወን ወስና እየተንቀሳቀሰች ነው ብለዋል።

ጂ ፎር የተሰኘው የኢትዮጵያ፣ የናይጀሪያ፣ አልጀሪያ እና ደቡብ አፍሪካ ስብስብ አዲስ ጉዳይ እንዳልሆነ ጠቅሰው÷ ከሌሎች አህጉራዊ እና ቀጠናዊ ተቋማት ጋር የሚጣረስ ነገር እንደሌለውም ነው ያነሱት።

በወንደሰን አረጋኸኝ