የሀገር ውስጥ ዜና

አጋር በሚል ስንገፋ የቆየን ድርጅቶች አሁን የውሳኔ ሰጪነት ዕድል አግኝተናል- አቶ አሻድሊ ሀሰን

By Feven Bishaw

March 11, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አጋር ፓርቲ በሚል ስንገፋ የቆየን ድርጅቶች አሁን የውሳኔ ሰጪነት ዕድል አግኝተናል ሲሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት ርዕሠ መስተዳድርና የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ አሻድሊ ሀሰን ገለጹ፡፡

አሸባሪው ህወሓት ስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት “አጋር ፓርቲ ናችሁ” በሚል ሰበብ በኢህአዴግ ጉባዔዎች እንዳንሳተፍ ስንገለል ቆይተናል ብለዋል።