አዲስ አበባ፣መጋቢት 2፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዶኔስክ ሪፐብሊክ ኃይሎች የዩክሬኗን የቮልኖቫካ ከተማ መቆጣጠራቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢጎር ኮናሼንኮቭ እንደገለፁት የዶኔትስክ ሪፐብሊክ ሃይሎች ቡድን የቮልኖቫካ ከተማን የተቆጣጠረ ሲሆን በአካባቢው የሚገኙትን የኦልጊንካ፣ ቬሊኮ-አናዶል፣ ዘሌኒ ጋይ ስፍራዎችንም መቆጣጠር መቻሉን ገልፀዋል።