አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ ጋር ተያይዞ የሚካሄዱ መርሃ ግብሮች ተጀምረው እስከሚጠናቀቁ ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደርገዋል፡፡
የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን÷ ጉባኤውን ተከትሎ የሚከናወኑ ልዩ ልዩ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ለማስቻል የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል ፡፡