የሀገር ውስጥ ዜና

ከብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ ጋር ተያይዞ የሚካሄዱ መርሃ ግብሮች ተጀምረው እስከሚጠናቀቁ ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

By Feven Bishaw

March 11, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ ጋር ተያይዞ የሚካሄዱ መርሃ ግብሮች ተጀምረው እስከሚጠናቀቁ ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደርገዋል፡፡

የብልፅግና ፓርቲ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ሲሆን÷ ጉባኤውን ተከትሎ የሚከናወኑ ልዩ ልዩ ተግባራት ስኬታማ ሆነው እንዲጠናቀቁ ለማስቻል የፀጥታ አካላት አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል ፡፡