አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላና በደቡብ ሱዳን ድንበር አካባቢ በተከሰተ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት በጋምቤላ ክልል ከ9 ሺህ 500 በላይ የላሬና የጂካዎ ወረዳ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን የክልሉ መንግስት አስታወቀ፡፡
የክልሉ መንግስት እንደገለጸው፥ በግጭቱ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ፥ በሰድስት ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን ታጣቂዎቹ የኢትዮጵያን እና የክልሉን ሰንደቅ ዓላማዎች እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶችን ዘርፈው ወስደዋል።