የሀገር ውስጥ ዜና

የነጃሺ ቀን በዱባይ ኤክስፖ 2020 ማዕከል ተከበረ

By Feven Bishaw

March 13, 2022

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በምትሳተፍበት ኤክስፖ 2020 ዱባይ ማዕከል “የነጃሺ ቀን” ፕሮግራም በዛሬው ዕለት ተከበረ።

በመርሀ ግብሩ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ ÷ ኢትዮጵያ የሁሉም እምነት ተከታዮች በጋራ የሚኖሩባት አገር መሆኗን ገልጸው፥ እስልምናም ይሁን ሌሎች እምነቶች የሰው ልጆች በሰላም እና በአንድነት ተሳስበው በወንድማማችነት አብረው እንዲኖሩ የሚያስተምሩ መሆኖቸውን አስረድተዋል።