ሁለተኛው ስምምነት ደግሞ የአንበሳ አውቶብስን አቅም የሚያዘምነውና የሚያሳድገው በኢንፎርሜሽን ኮሚዩኒኬሽን የታገዘው የብልህ ትራንስፖርት ስርዓት ከቻይናው ሺንዶ ሂሰንስ ትራንስ ቴክ ኩባንያ ጋር የተፈፀመ ውል ነው፡፡
ይህም ውል ከ14 ሚሊየን ዶላር በላይ እና በሃገር ውስጥ በተጨማሪ 9 ሚሊየን ብር ወጪ የሚደረግ ሲሆን÷ አጠቃላይ ድርጅቱን አለም ከደረሰበት የትራንስፖርት መሰረተ ልማት እድገት ጋር የሚያቀራርብና ከወረቀት ነፃ የሆነ አገልግሎት እንዲሁም ለደንበኞች በየተርሚናሉና የጉዞ ዲጂታል መረጃ አቀረርቦትም እንዲኖር የሚያደርግ ነው ተብሏል፡፡
በስምምነቱ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የከተማ አስተዳደሩ ለከተማ ድጋፍ ሰጪ አውቶብሶች ኪራይ ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ እንደሚደጉም ገልፀው የትራንስፖርት አገልግሎትን መንግስት ብቻውን የሚፈታው አይደለም ፤የግሉ ሴክተር አስተዋፅኦ ሊጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
እነዚህ ስምምነቶች የእውቀት ሽግግር እና ዘመናዊነትን አለም የደረሰበትን ቀልጣፋ የአይሲቲ አገልግሎትን ያካተተ መሰረታዊ የትራንስፖርት የለውጥ ስራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
ስምምነቱን ከተማውን አስተዳደሩን በመወከል የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሞገስ ጥበቡ ተፈራርመዋል፡፡