አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ናፍታሊ ቤኔት ጋር የሩሲያን እና የዩክሬንን ቀውስ በሰላማዊ መንገድ መፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በስልክ ተወያዩ።
ፕሬዜዳንት ፑቲን በሩሲያ እና በዩክሬን ተወካዮች መካከል በቪዲዮ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ስላለው ድርድር ለእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኔት ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።