አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ ትናንት ምሽት በተከሰተ የተሽከርካሪ እና የእሳት አደጋ የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ 230 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለፀ፡፡
የመኪና አደጋው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ትናንት ከምሽቱ 3 ሰዓት ከ14 ደቂቃ የደረሰ ሲሆን ÷ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪ አንድ ግሮሰሪ ውስጥ ጥሶ በመግባት ባደረገሰው አደጋ የ1 ሰው ህይወት አልፏል።